Skip to main content

Excel Academy

የኤክሴል አካዳሚ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የቅድመ መደበኛ ትምህርት ተማሪዎች የምርቃት መርሀ-ግብር በዛሬው ዕለት የወረዳው የትምህርት ቢሮ ተወካዮች፤ የአካዳሚው ቦርድ አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ሰኔ 27/2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ በአንጋንቱ ወረዳ ወይም በቀድሞው ቀበሌ 14 አዳራሽ ተከናወነ፡፡

ተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው በከፊል፤

ተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው በከፊል

በዕለቱ ከገንደ ኦዳ ቅርንጫፍ ት/ቤት ወንድ 87 ሴት 85 በአጠቃላይ 172 ተማሪዎች እንዲሁም ከቢፍቱ ቅርንጫፍ ት/ቤት ወንድ 70 ሴት 69 በአጠቃላይ 139 ተማሪዎች ሲሆኑ ከሁለቱም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የተመረቁት ተማሪዎች ብዛት በድምሩ 311 መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ተመራቂ ተማሪዎች ለታዳሚው የተለያዩ አዝናኝ ዝግጅቶችን ያቀረቡ ሲሆን ዋና ዋናዎቹም ትምህርታዊ ግጥሞች፤  መዝሙሮች፤ ባህላዊ ውዝዋዜዎች፤ መነባንቦች፤ ፋሺን ሾዎች ሲገኙበት በወላጆቻቸው ከፍተኛ አድናቆት ተለግሷቸዋል፡፡

በተመራቂ ተማሪዎች የቀረቡ የኦሮሞ ብሄረሰብ ባህላዊ የገዳ ምረቃት እና ውዝዋዜ፤

በመድረኩም የአካዳሚው የወላጅ ተወካይ ፓስተር ፍቃዱ ንጋቱ እንዲሁም የገንደ ኦዳ ቅርንጫፍ አፀደ ህፃናት ት/ቤት ርዕሰ መምህርት ወ/ሮ አዲስዓለም መተኪያ ለተመራቂ ተማሪዎች እና ወላጆቻቸው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በመጨረሻም ለተመራቂ ተማሪዎች የምስክር ወረቀት አሰጣጥ መርሀ-ግብር ተከናውኖ በተያዘለት መርሀ-ግብር መሰረት ከቀኑ 6፡00 ተጠናቋል፡፡

የአካዳሚው ወላጆች ተወካይ ፓስተር ፍቃዱ ንጋቱ መልዕክት ሲያስተላልፉ

Excel Academy Holds 2018 E.C. Pre-Primary School Graduation Ceremony

The graduation ceremony for the 2018 Ethiopian Academic Year Pre-Primary School students of Excel Academy was successfully held today, July 4, 2026, at the Angantu Hall Woreda (formerly Kebele 14 Hall) in a colorful and festive atmosphere. The event was attended by representatives of the Woreda Education Office, members of the Academy’s Board, invited guests, parents, and members of the school community.

Graduated Students and Their Family Picture Partially

During the ceremony, it was announced that 311 students graduated from the Academy’s two branch schools. Of these, 172 students graduated from the Gende Oda Branch School, comprising 87 boys and 85 girls, while 139 students graduated from the Biftu Branch School, including 70 boys and 69 girls.

Graduating Students Presenting Educational Poems

The graduating students delighted the audience with a variety of entertaining and educational performances. The program featured educational poems, songs, traditional dances, recitations, and fashion shows. Their outstanding performances earned them warm appreciation and enthusiastic applause from their parents and the invited guests.

Graduating Students Presenting Fashion Shows

During the ceremony, Pastor Fikadu Nigatu, the Academy’s Parent Representative, and Mrs. Addisalem Metekia, Principal of the Gende Oda Branch Kindergarten, delivered congratulatory messages to the graduates and their parents. They encouraged the students to pursue their education with dedication, confidence, and determination as they begin the next stage of their academic journey.

The event concluded with the presentation of graduation certificates to the students. The graduation ceremony was successfully completed according to the planned program and officially came to a close at 12:00 a.m.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *